በ1952 ዓ.ም የወጣው የንግድ ሕግ እንዲሁም የመድን ሥራ ፈቃድ ለመስጠት እና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ቁጥር 88/86 ተሽረው አዲስ ተሻሽሎ ከወጣው የንግድ ሕግ እና የመድን ሥራ ፈቃድ አዋጅ መሠረት በማድረግ የኩባንያችንን የመተዳደሪያ ደንብ እና መመሥረቻ ጽሑፍ ከሕጉ ጋር እንዲጣጣም ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ እንዲሁም የኩባንያውን (መነሻ) ዝቅተኛ የአክሲዮን ሽያጭ ጣሪያ ማስቀመጥ በማስፈለጉ ግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ.ም እና መጋቢት 27 ቀን 2017 ዓ.ም በተጠሩ 2 የተለያዩ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔዎች የኩባንያችንን መመሥረቻ ጽሑፍ ተሻሽሎ በሠነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ በቁጥር ቅ8/000978/40/2016 በ10/12/2015 እና ቅ12/ልዩ/0006040/4ለ/2017 ተመዝግቧል፡፡

