በ1952 ዓ.ም የወጣው የንግድ ሕግ እንዲሁም የመድን ሥራ ፈቃድ ለመስጠት እና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ቁጥር 88/86 ተሽረው አዲስ ተሻሽሎ ከወጣው የንግድ ሕግ እና የመድን ሥራ ፈቃድ አዋጅ መሠረት በማድረግ የኩባንያችንን የመተዳደሪያ ደንብ እና መመሥረቻ ጽሑፍ ከሕጉ ጋር እንዲጣጣም ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ እንዲሁም የኩባንያውን (መነሻ) ዝቅተኛ የአክሲዮን ሽያጭ ጣሪያ ማስቀመጥ በማስፈለጉ ግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ.ም እና መጋቢት 27 ቀን 2017 ዓ.ም በተጠሩ 2 የተለያዩ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔዎች የኩባንያችንን መመሥረቻ ጽሑፍ ተሻሽሎ በሠነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ በቁጥር ቅ8/000978/40/2016 በ10/12/2015 እና ቅ12/ልዩ/0006040/4ለ/2017 ተመዝግቧል፡፡
Category: Our News
የ32ኛው መደበኛ ጠቅላላ እና የ18ኛው አስቸኳይ ጉባኤ አጀንዳዎች

የስብሰባ ጥሪ

የ31ኛው መደበኛ ጠቅላላ እና የ17ኛው አስቸኳይ ጉባኤ አጀንዳዎች

ታህሳስ 20 ቀን 2016 ዓ.ም በተደረገው የባለአክሲዮኖች 30ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለቀጣይ ሶስት ዓመታት ኩባንያውን ለመምራት የተመረጡ የቦርድ አባላት ዝርዝር

የ30ኛው መደበኛ ጠቅላላ እና የ16ኛው አስቸኳይ ጉባኤ አጀንዳዎች

የ30ኛው መደበኛ ጠቅላላ እና የ16ኛው አስቸኳይ ጉባኤ አጀንዳዎች

እጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት
Details
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.
National Insurance Company of Ethiopia S.C.
ማስታወቂያ
በሥራ ላይ ያለው ቦርድ የሥራ ዘመን እ.ኤ. በ2023/2024 የሂሳብ ዓመት የሚያበቃ ወይም የሚጠናቀቅ በመሆኑ ቀጣዩን የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ለማከናወን ይቻል ዘንድ ኩባንያው በግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ/ም ባካሄደው የባአክስዮኖች 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት አስመራጭ ኮሚቴ መመረጡ ይታወሳል፡፡
በዚሁ መሠረት ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው የመልካም አስተዳደር መመሪያ ቁጥር SIB/48/2019 መሠረት እና በኩባንያው የዳይሬክተሮ ቦርድ የጥቆማ እና ምርጫ አሠራር መመሪያ መሠረት ለዳይሬክተሮች ቦርድ አባልነት ዕጩ ሆነው እንዲቀርቡ የተመረጡትን የተወዳዳሪ ባለአክስዮኖች ሥም ዝርዝር ለኢንሹራንስ ኩባንያው ባለአክስዮኖች እንደሚከተለው ይፋ አደርጓል፡፡
| ተ.ቁ. | የዕጩዎች ሙሉ ስም |
| 1 | ሻለቃ መርዕድ አባተ |
| 2 | አቶ መሠረት ወንድም |
| 3 | አሐዱ ባንክ አክስዮን ማህበር (ተወካይ አቶ ሰፊአለም ሊበን) |
| 4 | ካፒቴን የግዜሩ በለጠ |
| 5 | ፀሜክስ ግሎባል ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ ወ/ሮ ፀደኒያ ረዘነ) |
| 6 | ጀነራል መርካንታይል ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ አቶ ግርማ ከበደ) |
| 7 | ኢንጂ. ታምራት ኢዮብ |
| 8 | አቶ አብርሃም አጥላባቸው |
| 9 | አቶ አየለ አስፋወሰን |
| 10 | አቶ ዘውዱ አስታጥቄ |
| 11 | አቶ ደመረ ደምሴ |
| 12 | ዘመን ባንክ አ.ማ.(ተወካይ አቶ ደረጀ ዘበነ) |
| 13 | አቶ ታምራት ንቁ |
| ተ.ቁ | የተጠባባቂዎች ሙሉ ስም |
| 1 | ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል (ተወካይ አቶ እንደሻው ቦጌ) |
| 2 | ኦሞቲክ አጠቃላይ ንግ ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ አቶ ዓለማየሁ ተክሌ) |
| 3 | ብላክ ላየን ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ አቶ አብርሃም ኃ/መስቀል |
| 4 | ደ/ር ወርቅነህ አያሌው |
| 5 | ወ/ሮ ዛዲጓ ፀሐይ |
ማሳሰቢያ
ከላይ በሥም የተገለጹ ዕጩ የቦርድ አባልነት እንዳይወዳደሩ እና እንዳይመረጡ የሚያግድ (የማያስችል) ማስረጃ ካለ የተከበራችሁ ባለአክስዮኖች ማስታወቂያው በጋዜጣ በወጣ በ10 ቀናት ውስጥ በኩባንያው ዋና መ/ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 13 በመቅረብ እንድታስታወቁ ኮሚቴው በአክብሮት ይጠይቃል፡፡
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.
የዳሬክተሮ ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ
ሕዳር 19 ቀን 2016 ዓ/ም

እጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጥቆማ ለመቀበል የወጣ ማስታወቂያ
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. በስራ ላይ ያለው ቦርድ የስራ ዘመን እ.ኤ.አ.
በ2023/2024 የሂሳብ አመት የሚያበቃ ወይም የሚጠናቀቅ በመሆኑ ቀጣዩን የዳይሬክተሮች
ቦርድ አባላት ምርጫ ለማከናውን ይቻል ዘንድ ኩባንያው በግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው
የባለአክሲዮኖች 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት አስመራጭ መመረጡ
ይታወሳል፡፡
የጉባኤው ቃለ-ጉባኤም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ጸድቆ በሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ
አገልግሎት ጽ/ቤት የተመዘገበ በመሆኑ አስመራጭ ኮሚቴው ነሐሴ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. ስራውን
በይፋ ጀምሯል፡፡
በመሆኑም የኩባንያው ባለአክሲዮኖች ለኩባንያው ዕድገት አስተዋጽኦ ያደርጋሉ ብለው
የሚያምኑበትን ብቁ እጩዎች ከነሐሴ 14 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ህዳር 14 ቀን 2016
ዓ.ም. ድረስ እንዲጠቁሙ አስመራጭ ኮሚቴው በአክብሮት ይጋብዛል፡፡
በብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር ኤስ.አይ.ቢ. 32/2012 መሰረት ተጠቋሚ እጩዎች ማሟላት
ያለባቸው መስፈርቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
- የኩባንያው ባለአክሲዮን የሆነ/የሆነች፤
- የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ሆኖ ኩባንያውን በታማኝነት ለማገልግል ፈቃደኛ
የሆነ/የሆነች፤ - የኩባንያው ሰራተኛ ያልሆነ/ያልሆነች፤
- ዕድሜው/ዕድሜዋ ከ30 ዓመት ያላነሰ፤
- የኩባንያው አስመራጭ ኮሚቴ አባል ያልሆነ/ያልሆነች፤
- በሌላ የፋይናንስ ተቋም ውስጥ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ያልሆነ/ያልሆነች፤
- ከተጠቋሚዎች ውስጥ ቢያንስ 75 በመቶ ከታወቀ ዩኒቨርስቲ ወይም ተቋም የመጀመሪያ
ዲግሪ ያለው/ያላት እና ቀሪዎቹ 25 በመቶ ተጠቋሚዎች ቢያንስ የሁለተኛ ደረጃ
ትምህርት ያጠናቀቀ/ያጠናቀቀች፤ - የስራ ልምድን በተመለከተ በንግድ ስራ አስተዳደር፣ በኢንሹራንሰ፣ በኢኮኖሚክሲ፣ ሕግ፣
በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ የስራ ልምድ ያለው/ያላት ቢሆን ይመረጣል፤ - በአጠቃላይ በብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር ኤስ.አይ.ቢ. 32/2012 ስር የተመለከቱትን
የብቃት እና አግባብነት መመዘኛዎች የሚያሟላ/የምታሟላ፡፡
ማሳሰቢያ፡ - አንድ ባለአክሲዮን እስከ 9 ሰው መጠቆም ይችላል፡፡
- በሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት በቦርድ አባልነት ሲጠቆም ድርጅቱን ወክሎ በዳይሬክተርነት
የሚሰራውን ሰው አብሮ መጠቆም አለበት፡፡ - መስፈርቱን የሚያሟላ እና የቦርድ አባል ሆኖ ለማገልገል ፈቃደኛ የሆነ ባለአክሲዮን ራሱን
መጠቆም ይችላል፡፡ - መስፈርቱን የሚያሟሉ ሴት ባለአክሲዮኖች ይበረታታሉ፡፡
- ጠቋሚው ባለአክሲዮን ግለሰብ/ማኅበር/ድርጅት የሚጠቁመውን ባለአክሲዮን ፈቃደኝነት
አስቀድሞ ማወቅ አለበት፡፡ - የመጠቆሚያውን ቅፅ ደብረዘይት መንገድ፣ ዛፍኮ ሕንጻ፣ ሁለተኛ ፎቅ በሚገኘው የኩባንያው ዋና
መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 16 በመቅረብ ወይም ከኢንሹራንሱ ቅርንጫፍ ቢሮዎች ወይም ከኢንሹራንሱ
ድህረ ገፅ www.niceinsurance.et.com ማግኘት ይቻላል፡፡ - ለጥያቄ እና ማብራሪያ ኮሚቴው ፅ/ቤት በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥሮች 25114652448
ወይም 251-11-4661129 ወይም 251-11-4705378 በመደወል ወይም በኢሜል አድራሻ
nice@niceinsurance-et.com መጠየቅ ይቻላል፡፡ - የመጠቆሚያ ቅፁ በአግባቡ ተሞልቶ ከተፈረመ በኃላ፤ ማኅበር/ድርጅት ከሆነ ደግሞ ማህተም
ተደርጎበት በድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት ዛፍኮ ሕንጻ፣ ሁለተኛ ፎቅ በሚገኘው የኩባንያው ዋና
መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 16 በመቅረብ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ መክተት ይቻላል፡፡ - የመጠቆሚያ ቅፁ መመለሻ የመጨረሻ ቀን ህዳር 14 ቀን 2016 ዓ.ም. እስከ ቀኑ 6፡00 ሰዓት
ድረስ ነው፡፡ ከዚህ ቀን በኃላ የሚደርስ ጥቆማ ተቀባይነት የለውም፡፡
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.
የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ፡፡
የስብሰባ ጥሪ

