
የ31ኛው መደበኛ ጠቅላላ እና የ17ኛው አስቸኳይ ጉባኤ አጀንዳዎች

የኩባንያችን የአለም ገና ቅርንጫፍ ደንበኛ በሆኑት በአቶ ተሾመ መንግስቱ የግል ንብረት በሆነው የከባድ ጭነት መኪና(ሲኖትራክ) ላይ ታህሳስ 17 ቀን 2016 ዓ.ም በተፈጠረው ቃጠሎ ምክንያት በንብረታቸው ላይ ሙሉ በሙሉ ጉዳት ደርሷል፡፡
በዚህም መሰረት ከኩባንያችን በገዙት Political Violence and Terrorism (PVT) ( ውል መሰረት ሐምሌ 26 ቀን 2016 ዓ.ም የ 6,113,810 (ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ አስራ ሶስት ሺህ ስምንት መቶ አስር ብር) የካሳ ክፍያ ፈፅመናል፡፡
ኩባንያችን ብሔራዊ የኢትዮጰያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ ከዚህ ቀድም ሲጠቀምበት የነበረዉን የICT ቴክኖሎጅ በዘመናዊ ቴክኖሎጅ ለማዘመን ከ ARIMA INSURANCE SOFTWARE (W.L.L.) (“ARIMA”) ጋር የውል ስምምነት ሰኔ 22 ቀን 2016 ዓ.ም የተፈረመ ሲሆን የብሔራዊ የኢትዮጰያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ በመወከል የኩባንው ተጠባባቂ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አለምፀሃይ ደጋጋ እንዲሁም ARIMAን በመወከል አቶ ሞሀመድ ረመዳን በጋራ በመሆን የስምምነት ሰነዱን የፈረሙ ሲሆን በቅረቡ የሲሰተም የማበልፀግ እና የሙከራ ስራ ለመስራት ዝግጅት መጠናቀቁን አብስረዋል፡፡
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.
National Insurance Company of Ethiopia S.C.
ማስታወቂያ
በሥራ ላይ ያለው ቦርድ የሥራ ዘመን እ.ኤ. በ2023/2024 የሂሳብ ዓመት የሚያበቃ ወይም የሚጠናቀቅ በመሆኑ ቀጣዩን የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ለማከናወን ይቻል ዘንድ ኩባንያው በግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ/ም ባካሄደው የባአክስዮኖች 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት አስመራጭ ኮሚቴ መመረጡ ይታወሳል፡፡
በዚሁ መሠረት ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው የመልካም አስተዳደር መመሪያ ቁጥር SIB/48/2019 መሠረት እና በኩባንያው የዳይሬክተሮ ቦርድ የጥቆማ እና ምርጫ አሠራር መመሪያ መሠረት ለዳይሬክተሮች ቦርድ አባልነት ዕጩ ሆነው እንዲቀርቡ የተመረጡትን የተወዳዳሪ ባለአክስዮኖች ሥም ዝርዝር ለኢንሹራንስ ኩባንያው ባለአክስዮኖች እንደሚከተለው ይፋ አደርጓል፡፡
ተ.ቁ. | የዕጩዎች ሙሉ ስም |
1 | ሻለቃ መርዕድ አባተ |
2 | አቶ መሠረት ወንድም |
3 | አሐዱ ባንክ አክስዮን ማህበር (ተወካይ አቶ ሰፊአለም ሊበን) |
4 | ካፒቴን የግዜሩ በለጠ |
5 | ፀሜክስ ግሎባል ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ ወ/ሮ ፀደኒያ ረዘነ) |
6 | ጀነራል መርካንታይል ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ አቶ ግርማ ከበደ) |
7 | ኢንጂ. ታምራት ኢዮብ |
8 | አቶ አብርሃም አጥላባቸው |
9 | አቶ አየለ አስፋወሰን |
10 | አቶ ዘውዱ አስታጥቄ |
11 | አቶ ደመረ ደምሴ |
12 | ዘመን ባንክ አ.ማ.(ተወካይ አቶ ደረጀ ዘበነ) |
13 | አቶ ታምራት ንቁ |
ተ.ቁ | የተጠባባቂዎች ሙሉ ስም |
1 | ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል (ተወካይ አቶ እንደሻው ቦጌ) |
2 | ኦሞቲክ አጠቃላይ ንግ ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ አቶ ዓለማየሁ ተክሌ) |
3 | ብላክ ላየን ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ አቶ አብርሃም ኃ/መስቀል |
4 | ደ/ር ወርቅነህ አያሌው |
5 | ወ/ሮ ዛዲጓ ፀሐይ |
ማሳሰቢያ
ከላይ በሥም የተገለጹ ዕጩ የቦርድ አባልነት እንዳይወዳደሩ እና እንዳይመረጡ የሚያግድ (የማያስችል) ማስረጃ ካለ የተከበራችሁ ባለአክስዮኖች ማስታወቂያው በጋዜጣ በወጣ በ10 ቀናት ውስጥ በኩባንያው ዋና መ/ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 13 በመቅረብ እንድታስታወቁ ኮሚቴው በአክብሮት ይጠይቃል፡፡
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.
የዳሬክተሮ ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ
ሕዳር 19 ቀን 2016 ዓ/ም
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. በስራ ላይ ያለው ቦርድ የስራ ዘመን እ.ኤ.አ.
በ2023/2024 የሂሳብ አመት የሚያበቃ ወይም የሚጠናቀቅ በመሆኑ ቀጣዩን የዳይሬክተሮች
ቦርድ አባላት ምርጫ ለማከናውን ይቻል ዘንድ ኩባንያው በግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው
የባለአክሲዮኖች 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት አስመራጭ መመረጡ
ይታወሳል፡፡
የጉባኤው ቃለ-ጉባኤም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ጸድቆ በሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ
አገልግሎት ጽ/ቤት የተመዘገበ በመሆኑ አስመራጭ ኮሚቴው ነሐሴ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. ስራውን
በይፋ ጀምሯል፡፡
በመሆኑም የኩባንያው ባለአክሲዮኖች ለኩባንያው ዕድገት አስተዋጽኦ ያደርጋሉ ብለው
የሚያምኑበትን ብቁ እጩዎች ከነሐሴ 14 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ህዳር 14 ቀን 2016
ዓ.ም. ድረስ እንዲጠቁሙ አስመራጭ ኮሚቴው በአክብሮት ይጋብዛል፡፡
በብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር ኤስ.አይ.ቢ. 32/2012 መሰረት ተጠቋሚ እጩዎች ማሟላት
ያለባቸው መስፈርቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
ለብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. ባለአክሲዮኖች በሙሉ
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አክሲዮን ማኅበር ዋና መ/ቤቱ በቂርቆስ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 04፣ የቤት ቁጥር 894 የሚገኝና የንግድ ምዝገባ ቁጥሩ13-1543/87 ሲሆን የማኅበሩ ዋና ገንዘብም ብር 250 ሚሊዮን የተፈቀደ እና ብር 228 ሚሊዮን የተከፈለ ነው፡፡
ማኅበሩ የባለአክሲዮኖችን 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 15ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ቅዳሜ፣ ህዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም. በሂልተን ሆቴል (Hilton Hotel) ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ሆኖም ግን የጉባኤው ቃለጉባኤዎች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኢንሹራንስ ሱፐርቪዥን ዳይሬክቶሬት ውድቅ በመደረጋቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ትእዛዝ መሰረት ጉባኤዎቹን በድጋሚ መጥራት አስፈልጓል፡፡
በመሆኑም የኩባንያው ባለአክሲዮኖች በሙሉ ቅዳሜ ፣ ግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ከጠዋቱ በ2፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል (Inter Luxury Hotel) በድጋሚ በሚካሄደው 30ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 16ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንዲገኙ በኢትዮጵያ ንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 አንቀፅ 367/2 መሰረት የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የ30ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች
የ16ኛው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች
ማሳሰቢያ፡
የዳይሬክተሮች ቦርድ
NICE is the first wholly privately owned insurance company, established in post – 1994 Ethiopia, to engage in general insurance business…
Address: Debre Zeit Road ZEFCO Building Kirkos sub-city K.05/06/07 H.No 894
Phone : +251 11 4 705 378/
+251 11 4 704 967
Fax : +251 11 465 0660
P.O.Box: 12645 Addis Ababa, Ethiopia
E-mail: info@niceinsurance-et.com