እጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት

Details

ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.

National Insurance Company of Ethiopia S.C.

ማስታወቂያ

በሥራ ላይ ያለው ቦርድ የሥራ ዘመን እ.ኤ. በ2023/2024 የሂሳብ ዓመት የሚያበቃ ወይም የሚጠናቀቅ በመሆኑ ቀጣዩን የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ለማከናወን ይቻል ዘንድ ኩባንያው በግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ/ም ባካሄደው የባአክስዮኖች 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት አስመራጭ ኮሚቴ መመረጡ ይታወሳል፡፡

በዚሁ መሠረት ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው የመልካም አስተዳደር መመሪያ ቁጥር SIB/48/2019 መሠረት እና በኩባንያው የዳይሬክተሮ ቦርድ የጥቆማ እና ምርጫ አሠራር መመሪያ መሠረት ለዳይሬክተሮች ቦርድ አባልነት ዕጩ ሆነው እንዲቀርቡ የተመረጡትን የተወዳዳሪ ባለአክስዮኖች ሥም ዝርዝር ለኢንሹራንስ ኩባንያው ባለአክስዮኖች እንደሚከተለው ይፋ አደርጓል፡፡

ተ.ቁ.የዕጩዎች ሙሉ ስም
1ሻለቃ መርዕድ አባተ
2አቶ መሠረት ወንድም
3አሐዱ ባንክ አክስዮን ማህበር (ተወካይ አቶ ሰፊአለም ሊበን)
4ካፒቴን የግዜሩ በለጠ
5ፀሜክስ ግሎባል ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ ወ/ሮ ፀደኒያ ረዘነ)
6ጀነራል መርካንታይል ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ አቶ ግርማ ከበደ)
7ኢንጂ. ታምራት ኢዮብ
8አቶ አብርሃም አጥላባቸው
9አቶ አየለ አስፋወሰን
10አቶ ዘውዱ አስታጥቄ
11አቶ ደመረ ደምሴ
12ዘመን ባንክ አ.ማ.(ተወካይ አቶ ደረጀ ዘበነ)
13አቶ ታምራት ንቁ
ተ.ቁየተጠባባቂዎች ሙሉ ስም
1ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል (ተወካይ አቶ እንደሻው ቦጌ)
2ኦሞቲክ አጠቃላይ ንግ ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ አቶ ዓለማየሁ ተክሌ)
3ብላክ ላየን ሀላ/የተ/የግ/ማ (ተወካይ አቶ አብርሃም ኃ/መስቀል
4ደ/ር ወርቅነህ አያሌው
5ወ/ሮ ዛዲጓ ፀሐይ

ማሳሰቢያ

ከላይ በሥም የተገለጹ ዕጩ የቦርድ አባልነት እንዳይወዳደሩ እና እንዳይመረጡ የሚያግድ (የማያስችል) ማስረጃ ካለ የተከበራችሁ ባለአክስዮኖች ማስታወቂያው በጋዜጣ በወጣ በ10 ቀናት ውስጥ በኩባንያው ዋና መ/ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 13 በመቅረብ እንድታስታወቁ ኮሚቴው በአክብሮት ይጠይቃል፡፡

ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.

የዳሬክተሮ ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ

ሕዳር 19 ቀን 2016 ዓ/ም

እጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጥቆማ ለመቀበል የወጣ ማስታወቂያ


ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. በስራ ላይ ያለው ቦርድ የስራ ዘመን እ.ኤ.አ.
በ2023/2024 የሂሳብ አመት የሚያበቃ ወይም የሚጠናቀቅ በመሆኑ ቀጣዩን የዳይሬክተሮች
ቦርድ አባላት ምርጫ ለማከናውን ይቻል ዘንድ ኩባንያው በግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው
የባለአክሲዮኖች 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት አስመራጭ መመረጡ
ይታወሳል፡፡
የጉባኤው ቃለ-ጉባኤም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ጸድቆ በሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ
አገልግሎት ጽ/ቤት የተመዘገበ በመሆኑ አስመራጭ ኮሚቴው ነሐሴ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. ስራውን
በይፋ ጀምሯል፡፡
በመሆኑም የኩባንያው ባለአክሲዮኖች ለኩባንያው ዕድገት አስተዋጽኦ ያደርጋሉ ብለው
የሚያምኑበትን ብቁ እጩዎች ከነሐሴ 14 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ህዳር 14 ቀን 2016
ዓ.ም. ድረስ እንዲጠቁሙ አስመራጭ ኮሚቴው በአክብሮት ይጋብዛል፡፡
በብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር ኤስ.አይ.ቢ. 32/2012 መሰረት ተጠቋሚ እጩዎች ማሟላት
ያለባቸው መስፈርቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡

  1. የኩባንያው ባለአክሲዮን የሆነ/የሆነች፤
  2. የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ሆኖ ኩባንያውን በታማኝነት ለማገልግል ፈቃደኛ
    የሆነ/የሆነች፤
  3. የኩባንያው ሰራተኛ ያልሆነ/ያልሆነች፤
  4. ዕድሜው/ዕድሜዋ ከ30 ዓመት ያላነሰ፤
  5. የኩባንያው አስመራጭ ኮሚቴ አባል ያልሆነ/ያልሆነች፤
  6. በሌላ የፋይናንስ ተቋም ውስጥ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ያልሆነ/ያልሆነች፤
  7. ከተጠቋሚዎች ውስጥ ቢያንስ 75 በመቶ ከታወቀ ዩኒቨርስቲ ወይም ተቋም የመጀመሪያ
    ዲግሪ ያለው/ያላት እና ቀሪዎቹ 25 በመቶ ተጠቋሚዎች ቢያንስ የሁለተኛ ደረጃ
    ትምህርት ያጠናቀቀ/ያጠናቀቀች፤
  8. የስራ ልምድን በተመለከተ በንግድ ስራ አስተዳደር፣ በኢንሹራንሰ፣ በኢኮኖሚክሲ፣ ሕግ፣
    በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ የስራ ልምድ ያለው/ያላት ቢሆን ይመረጣል፤
  9. በአጠቃላይ በብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር ኤስ.አይ.ቢ. 32/2012 ስር የተመለከቱትን
    የብቃት እና አግባብነት መመዘኛዎች የሚያሟላ/የምታሟላ፡፡
    ማሳሰቢያ፡
  10. አንድ ባለአክሲዮን እስከ 9 ሰው መጠቆም ይችላል፡፡
  11. በሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት በቦርድ አባልነት ሲጠቆም ድርጅቱን ወክሎ በዳይሬክተርነት
    የሚሰራውን ሰው አብሮ መጠቆም አለበት፡፡
  12. መስፈርቱን የሚያሟላ እና የቦርድ አባል ሆኖ ለማገልገል ፈቃደኛ የሆነ ባለአክሲዮን ራሱን
    መጠቆም ይችላል፡፡
  13. መስፈርቱን የሚያሟሉ ሴት ባለአክሲዮኖች ይበረታታሉ፡፡
  14. ጠቋሚው ባለአክሲዮን ግለሰብ/ማኅበር/ድርጅት የሚጠቁመውን ባለአክሲዮን ፈቃደኝነት
    አስቀድሞ ማወቅ አለበት፡፡
  15. የመጠቆሚያውን ቅፅ ደብረዘይት መንገድ፣ ዛፍኮ ሕንጻ፣ ሁለተኛ ፎቅ በሚገኘው የኩባንያው ዋና
    መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 16 በመቅረብ ወይም ከኢንሹራንሱ ቅርንጫፍ ቢሮዎች ወይም ከኢንሹራንሱ
    ድህረ ገፅ www.niceinsurance.et.com ማግኘት ይቻላል፡፡
  16. ለጥያቄ እና ማብራሪያ ኮሚቴው ፅ/ቤት በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥሮች 25114652448
    ወይም 251-11-4661129 ወይም 251-11-4705378 በመደወል ወይም በኢሜል አድራሻ
    nice@niceinsurance-et.com መጠየቅ ይቻላል፡፡
  17. የመጠቆሚያ ቅፁ በአግባቡ ተሞልቶ ከተፈረመ በኃላ፤ ማኅበር/ድርጅት ከሆነ ደግሞ ማህተም
    ተደርጎበት በድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት ዛፍኮ ሕንጻ፣ ሁለተኛ ፎቅ በሚገኘው የኩባንያው ዋና
    መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 16 በመቅረብ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ መክተት ይቻላል፡፡
  18. የመጠቆሚያ ቅፁ መመለሻ የመጨረሻ ቀን ህዳር 14 ቀን 2016 ዓ.ም. እስከ ቀኑ 6፡00 ሰዓት
    ድረስ ነው፡፡ ከዚህ ቀን በኃላ የሚደርስ ጥቆማ ተቀባይነት የለውም፡፡
    ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.
    የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ፡፡

የስብሰባ ጥሪ

   

ለብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ .. ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አክሲዮን ማኅበር ዋና መ/ቤቱ በቂርቆስ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 04፣ የቤት ቁጥር 894 የሚገኝና የንግድ ምዝገባ ቁጥሩ13-1543/87 ሲሆን የማኅበሩ ዋና ገንዘብም ብር 250 ሚሊዮን የተፈቀደ እና ብር 228 ሚሊዮን የተከፈለ ነው፡፡

ማኅበሩ የባለአክሲዮኖችን 29ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 15ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ቅዳሜ፣ ህዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም.  በሂልተን ሆቴል (Hilton Hotel) ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ሆኖም ግን የጉባኤው ቃለጉባኤዎች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኢንሹራንስ ሱፐርቪዥን ዳይሬክቶሬት ውድቅ በመደረጋቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ትእዛዝ መሰረት ጉባኤዎቹን በድጋሚ መጥራት አስፈልጓል፡፡

በመሆኑም የኩባንያው ባለአክሲዮኖች በሙሉ ቅዳሜ ፣ ግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ከጠዋቱ በ2፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል (Inter Luxury Hotel) በድጋሚ በሚካሄደው 30ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 16ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንዲገኙ በኢትዮጵያ ንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 አንቀፅ 367/2 መሰረት የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

30ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች

  1. የ30ኛውን መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎችን ማፅደቅ፤
  2. የ29ኛውን መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎችን መሻር፤
  3. የተደረጉ የአክስዮን ዝውውሮችን/ድልድሎች፣ ስጦታዎችን እና ሽያጮችን ተቀብሎ ማፅደቅ፤
  4. እ.ኤ.አ. የ2021/2022 በጀት አመት የዳይሬክተሮች ቦርድ ዓመታዊ የስራ ክንውን ሪፖርትን ማዳመጥ፤
  5. እ.ኤ.አ. የ2021/2022 በጀት አመት የውጪ ኦዲተሮችን ሪፖርት እና የሂሳብ መግለጫዎችን ማዳመጥ፤
  6. በተራ ቁጥር 3 እና 4 በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ተወያይቶ መወሰን፤
  7. እ.ኤ.አ. የ2021/2022 በጀት አመት የተጣራ ትርፍ አደላደል እና አከፋፈልን አስመልክቶ የዳይሬክተሮች ቦርድ ባቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ተወያይቶ መወሰን፤
  8. እ.ኤ.አ. የ2022/2023 በጀት አመት የውጪ ኦዲተሮች መምረጥ እና የስራ ዋጋቸውን ተወያይቶ መወሰን፤
  9. የዳይሬክተሮች ቦርድ እ.ኤ.አ. የ2021/2022 በጀት አመት ዓመታዊ ክፍያን እና የ2022/2023 በጀት አመት ወርሃዊ አበል ላይ ተወያይቶ መወሰን፤
  10. የአስመራጭ ኮሚቴ አባላትን ክፍያ መወሰን፤
  11. እ.ኤ.አ. ለ2023/2024 በጀት አመት ስለሚደረገው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ የአስመራጭ ኮሚቴ አባላትን መምረጥ፤
  12. የመደበኛ ጠቅላላ ጉባኤን ቃለጉባኤ ማፅደቅ፡፡

16ኛው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች

  1. የ16ኛውን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎችን ማፅደቅ፤
  2. የ15ኛውን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎችን መሻር፤
  3. የኩባንያውን ካፒታል ለማሳደግ በ14ኛው ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተላለፈውን የክፍያ ጊዜ ውሳኔ በተመለከተ ተወያይቶ መወሰን፤
  4. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እ.ኤ.አ. በሴፕቴምበር 15 ቀን 2022 ባወጣው መመሪያ (Directive Number SIB 57/2022) መሰረት የኩባንያውን የተከፈለ ካፒታል ስለማሳደግ ተወያይቶ መወሰን፤
  5. የኩባንያውን የመመስረቻ ጽሑፍ ስለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ ላይ ተወያይቶ መወሰን፤
  6. የአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን ቃለጉባኤ ማፅደቅ፡፡

ማሳሰቢያ፡

  1. በጉባኤው ላይ በአካል ለመገኘት የማይችሉ ባለአክሲዮኖች ተወካይ በመሰየም መሳተፍ ይችላሉ፡፡ ለዚህም ጉባኤው ከሚካሄድበት ቀን ቢያንስ ከ3 የሥራ ቀናት በፊት በኩባንያው ዋና መ/ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 13 (ቦርድ ክፍል) በመቅረብ የተዘጋጀውን የውክልና መስጫ ቅፅ በመፈረም ወይም በሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት ጽ/ቤት ተረጋግጦ የተሰጠ የውክልና ስልጣን ማስረጃ ዋናውን እና አንድ ኮፒ በስብሰባው ዕለት ይዞ በመቅረብ መሳተፍ ይቻላል፡፡
  • ባለአክሲዮኖችም ሆኑ ተወካዮች ወደ ስብሰባው ቦታ ሲመጡ የራሳቸውን የታደሰ መታወቂያ ካርድ ወይም የታደሰ ፓስፖርት ወይም የታደሰ መንጃ ፈቃድ ዋናውን እና ኮፒ ይዘው መቅረብ እንዳለባቸው እናሳስባለን፡፡
  • ተወካዮች የውጪ ሀገር ዜግነት ያላቸው ከሆኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ እንዲያቀርቡ እንጠይቃልን፡፡

የዳይሬክተሮች ቦርድ

የስብሰባ ጥሪ

ለተከበራችሁ የብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ.) ባለአክሲዮኖች

የባለአክሲዮኖች 29ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 15ኛው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ቅዳሜ ህዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ይካሄዳል፡፡ የጉባኤው አጀንዳዎችም እሁድ ጥቅምት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ታትሞ ወጥቷል፡፡ በመሆኑም ይህንኑ አውቃችሁ በእለቱ በጉባኤው ላይ እንድትገኙ የዳይሬክሮች ቦርድ የአክብሮት ጥሪውን ያቀርባል፡፡

የብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ.) የዳይሬክተሮች ቦርድ

NICE is the first wholly privately owned insurance company, established in post – 1994 Ethiopia, to engage in general insurance business…

Contact Info

Address: Debre Zeit Road ZEFCO Building Kirkos sub-city K.05/06/07 H.No 894
Phone : +251 11 4 705 378/
+251 11 4 704 967
Fax : +251 11 465 0660
P.O.Box:  12645  Addis Ababa, Ethiopia
E-mail: info@niceinsurance-et.com

YouTube
LinkedIn
Share